የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ
ብልፅግና ፓርቲ በሀገሪቱ የዳበረ ኢኮኖሚ ለመገንባት፣ ማኀበራዊ ፍትህ ለማንገስና እውነተኛ ዴሞክራሲን ለማስፈን ባለፉት ሁለት ዓመታት በተወሰዱ ተጨባጭ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ እርምጃዎች ፍሬም ተስፋም ያለበት ነባራዊ ሀገራዊ ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ለውጡ ማዕከላዊ ግቦች የነበረዉና ያለዉ ማለትም ማዕከላዊ ግቦቹም የሃገረ መንግስት ግንባታ፥ ብሄረ መንግስት ግንባታና የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ በማጠናከር ፍትሕ የሰፈነባት፣ በዴሞክራሲ የዳበረች፣ በሰብአዊ መብት ጥበቃ የተመሰከረላት፣ በኢኮኖሚ የበለጸገች፣ በሰላምና በደኅንነት የተረጋጋች ሀገር ማድረግ መሆኑ እና እነዚህ ጉዳዮች ደግሞ የሀገራችን የፖለቲካ ስብራቶች ሚስጥርና እንቆቅልሽ መፍቻዉም መሆኑን የተገነዘበው ህዝባችን ለዉጡን በጽኑ ደግፎ ቆሟል ብቻ ሳይሆን የለዉጥ አደናቃፊ ሃይሎች የፈጠሩትን ሴራ እና የሚደረድሩትን ወንጀሎን ሁሉ በጽናት በመቋቋምና በመከላከል ለፓርቲያችን አጋርነቱን እያረጋገጠ ይገኛል። በመሆኑም ፓርቲያችን እንደ መሪ የፖለቲካ ፓርቲ በተለይ በዚህ ወቅት የኮሮናን ወረርሽን በመከላከል ለህዝቡ ያለዉን ዉግንና ማረጋገጥ ይገባዋል፡፡ እንዲሁም የሀገራችን ህዝቦች የጋራ ማህተም የሆነዉን ታላቁ የህዳሴን ግድብ ማጠናቀቅ የሚያስችል የህዝብ ንቅናቄ የመፍጠር፤ ምርጫዉ ሰላማዊ እና ተዓማኒነት ያለዉ እንዲሁም በፓርቲያችን አሸናፊነት የሚጠናቀቅ እንዲሆን የማድረግ፤ ሰላማችንን የሚያረጋግጥ ጠንካራ የፖለቲካ ስራ የማከናወን፤ በገጠርና በከተማ የህዝቡን ህይወት የሚቀይሩ ተግባራት ላይ በማተኮር፤ የወጣቶችና የሴቶችን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ስራዎች ላይ በመረባረብ እና ህዝባችንን ሊያማርሩ የሚችሉ የመልካም አስተዳደር እጦትና ሌብነት ላይ የተለየ የፖለቲካ ርብርብ በማድረግ የለዉጡን ቀጣይነትና ዉጤታማነት የሚያረጋግጡ ተግባራትን በተለየ ድስፕሊንና ከፍ ባለ ዉግንና መፈጸም ይገባል፡፡ ሀገራዊ ለውጡ እና ለውጡን የሚመራው ፓርቲያችን ይዞት የመጣውን አዲስ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊና የውጪ ግንኙነት እሳቤ በመረዳት ረገድ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመቅረፍ ረገድ እስካሁን የተሰጡ ስልጠናዎች እና የተግባቦት ስራዎቻችን የራሳቸውን ሚና መጫወታቸው እንዳለ ሆኖ በየወቅቱ በሚሰጠዉ ስልጠና ላይ ደግሞ እነዚህን ብዥታዎች ለማጥራትና የተሟላ ግልፅነት ለመፍጠር አቅደን በመስራታችን አባላት በራስ መተማመን እንዲጎለብት ሆኗል፡፡
ዋና ዓላማ ፥

የፓርቲውን ሰብዓዊና ቁሳዊ ሀብት አቀናጅቶ ለመምራት፣ ውጤታማ የዕቅድ አፈፃፀም ለማስመዝገብና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ነው፡፡
ዝርዝር ዓላማዎች ፥

-ለተገልጋዩ ህብረተሰብ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት እንዲሁም መልካም አስተዳደርን በማስፈን የተገልጋይ እርካታና አመኔታ ለማሳደግ፣
-የጽ/ቤቱ ሰራተኞች ይህንን ዕቅድ ለማሳካት ሙሉ አቅማቸዉን በመጠቀም በቁርጠኝነት እንድንቀሳቀሱ ለማድረግ፣
-ዕቅዱን መነሻ በማድረግ አፈጻጸሙን ለመከታተል እንዲሁም አፈጻጸሙን በየጊዜዉ በመገምገም ጥንካሬንና ድክመትን በመፈተሽ ጠንክሮ በመስራት ጥሩ ዉጤት ለማስመዝገብ ፣
ፓርቲውን በዕቅድ የተመራ በማድረግ የተቋሙን ተልዕኮ ውጤታማነትና ስኬታማነት ማረጋገጥ፡፡

አግኙን

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

የብልጽግና ፓርቲ የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ብዝሃነትና አስተዋፅዖ እውቅና የሚሰጥ እውነተኛ ፌዴራላዊ ሥርዓት ለማጠናከር እና ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኛ ነው።

አግኙን



የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት



ዋና ዓላማ


"የበለጸገች ወላይታን እውን ማድረግ"

የፓርቲያችን ጥቅል ዓላማ የበለጸገች ወላይታን እውን ማድረግ ነው።ስንል ፈርጀ ብዙ ትርጓሜን አዝሎ የኢኮኖሚ፣ፖለቲካ እና ማኅበራዊ ገጽታ ያለው ነው።

ተልዕኮ


ፓርቲው በዞኑ ያሉትን ሰብዓዊና ተፈጥሯዊ ሀብቶች አቀናጅቶ በመምራት፣ ቀጠይነት ባለዉ መልኩ በስፋት ጥቅም ላይ በማዋልና እንዲሁም የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦችን አንድነት በማጠናከርና የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን በማፋጠን መልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ወደ ላቀ ደረጃ እንድደርስ ማድረግ፤

ራዕይ


ከ2013-2023 ዓ.ም ለብልጽግና የምተጉ አባላትንና አመራርን በትጋት በመመልመል ዘላቅ አመራር እያፈሩ ለክልልና ለሀገር ደርጃ የሚሆኑ ብቁ አመራር ተፈጥሮ መየት፤

እሴቶች


ከ2013-2023 ዓ.ም ለብልጽግና የምተጉ አባላትንና አመራርን በትጋት በመመልመል ዘላቅ አመራር እያፈሩ ለክልልና ለሀገር ደርጃ የሚሆኑ ብቁ አመራር ተፈጥሮ መየት፤



መልዕክቶች

ከወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት







የፌስቡክ ገፃችን